Friday, December 12, 2014

ባለፈው ዓመት ከሳዑዲ አረቢያ ከተባረሩት ኢትዮጵያውያን መካከል 85ሺው ተመልሰው መሄዳቸው ተዘገበ


ባለፈው ዓመት ከሳውዲ አረብያ ከተባረሩት ከአንድ መቶ ሰባ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን 50% (ከ 85ሺህ በላይ የሚሆኑት) ተመልሰው ሳውዲ አረብያ መግባታቸውን አዲስ አበባ ላይ ዛሬ በወጣ አዲስ የዳሰሳ ጥናት ተገለፀ:: (የጉዳያችን አጭር ጥንቅር)

ዛሬ የክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማኅበር (CRDA) በሳውዲ ተመላሾች አሁን ያሉበት ጉዳይ ላይ የሚወያይ አውደ ጥናት አዲስ አበባ ላይ የቀረበ አንድ ጥናት ባለፈው ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ከተባረሩት ከአንድ መቶ ሰባ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን 50% (ከ 85ሺህ በላይ የሚሆኑት) ተመልሰው ሳውዲ አረብያ መግባታቸውን ይገልፃል።ቪኦኤ የአሜሪካ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት ዘጋቢ ከአዲስ አበባ አውደ ጥናቱን አስመልክቶ ባቀረበው ዘገባ የክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማኅበር (CRDA) የስትራቴጂክ ቡድን መሪ እና በድርጅቱ ልዩ አማካሪ አቶ ክፍለ ማርያም ገ/ወልድን ባነጋገረበት ወቅት ”ሀቁን እንነጋገር ከተባለ ግማሾቹ ተመልሰው ሄደዋል” ብለዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙ የስደት ተመላሾች ውስጥ ለቪኦኤ ሃሳቧን የሰጠች ወጣት ”ከችግር የተነሳ ነው።እዚህ ሆኘ እራሴን ከማጠፋ ሄጄ ልሙት ከማለት ነው” ብላለች።ለወገኖቻችን በአራቱም ማዕዘን መውጣት የሀገራችን አጠቃላይ የፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ከዋና ምክንያትነት አያመልጡም።የችግሩ ዋና መንስኤ እየተተወ ስደቱን ብቻ ብናወጋው መፍትሄ አይሆንም።
የተመላሾቹንም ሆነ የአዲሱን ትውልድ በሀገሩ ተመክቶ እና ተማምኖ እንዲኖር አልተደረገም።ይልቁንም የኢህአዲግ አባል ካልሆነ እና ከካድሬዎች እግር ስር ካለወደቀ መኖር አይችልም።በሥራ ዓለም ያለው ባለሙያንም ብንመለከት የነፃነት ማጣቱ እና ሃሳቡን እና ችሎታውን ለሀገሩ ማበርከት አልቻለም።መሃንዲሱ፣የህክምና ዶክተሩ እና የአይሮፕላን አብራሪው በሀገሩ ተስፋ እንዲቆርጥ ተደረገ።ሁሉ ሃገሩን ጥሎ ለመሄድ አኮበኮበ የቀረው ቆርጦ ከኢህአዴግ/ወያኔ ጋር ተጋፈጠ።ለእዚህ አብነት የሚሆኑን የሰማያዊ ፓርቲ እና የዘጠኙ አጋሮቻቸው ድርጊት ተጠቃሽ ነው።
የኢትዮጵያ ጉዳይ በእንዲህ አይነት ሁኔታ እንደሀገር የመቀጠላችን አደጋ በራሱ በግልፅ ይታያል።ጥቂቶች በሙስና እና በጎሳቸው ብቻ በሀብት ሲናጥጡ ሌላው ዜጋ ሃገሩን በረሃ ለበረሃ እየተንከራተተ ሲወጣ አይኖርም።አንድ ቀን እዝያው ሀገር ውስጥ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ የመውጣታቸው አደጋ አይኖርም ማለት አይቻልም።የወገኖቻችን ሀገር ጥለው የመሄድ ጉዳይ የሚያመለክተው ይህንን ነው።ቁጥር ደግሞ ከሁሉ በላይ የሀገራችንን የፖለቲካ መድረክ መቀየር እንዳለበት አመላካች ነው።”ከሰማንያ ሺህ በላይ የሚሆኑ ወደ ሀገር ቤት የተመለሱ ወገኖቻችን ተመልሰው መከራ ወደ አዩባት ሳውዲ ተመለሱ” የሚለው ዘገባ በእራሱ መጪውን አመላካች ነው።እናት ልጇ ተመልሳ እቤት ከገባች በኃላ ተመልሳ ስትሰደድ እንዴት ታዝን? ምን ያልደረሰብን አለ? ሱዳን ባቅሟ ኢትዮጵያውያንን አባረረች ስንባል፣የመን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መንገዶቿን ሞሉ ሲባል፣ጅቡቲ ኢትዮጵያንን ስታስር፣ እራሳችንን መጠየቅ ያሉብን ሶስት ጥያቄዎች አሉ እነሱም –
ኢትዮጵያ ክብሯ እና ማንነቷ አልተዋረደም ወይ?
ያለውን አስከፊ ሁኔታ ለመቀየር የፖለቲካው ችግር አለመስተካከል ዋነኛው ምክንያት አይደለም ወይ? እና
ለእዚህም ተጠያቂዎች የእያንዳንዳችን ለስርዓቱ መቀየር የአቅማችንን አለማድረግ አይደለም ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች።
በመሆኑም ሰቆቃ ስንሰማ የምንኖርበት ዘመን እንዲቆም፣ኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ፣በሙስና የተነከረው እና ክብሯን እና ማንነቷን ከሚመጥናት በታች የሆነ አስተሳስብ ያለው ኢህአዲግ/ወያኔ የበለጠ ሀገራችንን መቀመቅ ሳይከት የእያንዳንዳችንን ኃላፊነት እንወጣ።በዝምታችን ኢትዮጵያን ከሚገድሉ ጋር አንተባበር።

Wednesday, December 10, 2014

የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ መንግሥት ከምዕራብ የፋይናንስ ተቋማት እንዲበደር አሳሰቡ፡፡


  • 200
     
    Share
World-Bankየዓለም ባንክና የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ በጻፉት ደብዳቤ፣ መንግሥት ለካፒታል ፕሮጀክቶች ከአንድ የገንዘብ ምንጭ ብቻ መበደር እንደሌለበትና ይልቁኑም ለምዕራብ የገንዘብ ተቋማት በሩን ክፍት ሊያደርግ እንደሚገባ ምክረ ሐሳብ ለገሱ፡፡
ሁለቱ ግዙፍ የገንዘብ ተቋማት በኅዳር ወር መጨረሻ ከዋሽንግተን ለገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በጋራ በጻፉት ደብዳቤ፣ በርካታ የአውሮፓ ባንኮች የኢትዮጵያ መንግሥት ለሚያካሂዳቸው ፕሮጀክቶች ብድር ለመስጠት ፍላጎት እያሳዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ነገር ግን መንግሥት በቂ ድርድር በማድረግ የሚቀርብለትን ፋይናንስ መጠቀም ሲገባው፣ ፈጣን ምላሽ አለመስጠቱንና ከአንድ ምንጭ ብቻ መጠቀሙን (የቻይና መንግሥት) ደብዳቤው ጠቁሞ፣ አንድ የገንዘብ ምንጭ ላይ ብቻ ትኩረት ማድረጉ ጉዳት እንዳለው ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡
በአንፃሩ የጀርመን፣ የእስራኤልና የእንግሊዝ ባንኮች ለኢትዮጵያ ፋይናንስ ለማቅረብ ዝግጁ ቢሆኑም የመንግሥትን ትኩረት አለማግኘታቸው ተጠቁሟል፡፡
የሁለቱ የፋይናንስ ተቋማት ደብዳቤ መንግሥት በቅርቡ ቦንድ ለዓለም ገበያ ማቅረቡን መልካም ጅማሬ መሆኑን ጠቅሶ፣ ከዚህ በበለጠ ምዕራባዊ ባንኮችን ሊጠቀም እንደሚገባና አንድን የገንዘብ ምንጭ ብቻ መጠቀም ጉዳት ሊኖረው እንደሚችል ይገልጻል፡፡
ክሬዲት ስዊስ፣ በርክሌ፣ ጄፒ ሞርጋንና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የመሳሰሉ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ መንግሥት ፕሮጀክቶች ፋይናንስ ለማቅረብ ፍላጎት አሳይተዋል፡፡ ሁለቱ የገንዘብ ተቋማት በኢትዮጵያ የፋይናንስ ግኝቶች ላይ ግምገማ ማካሄዳቸውን ገልጸው፣ የንግድና የካፒታል ፕሮጀክቶች ብድሮች ሙሉ ለሙሉ ማለት በሚያስችል ሁኔታ በአንድ የገንዘብ ምንጭ ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸውን በግምገማቸው መረዳታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ተቋማቱ መንግሥት የዕዳ አስተዳደሩን መቀየጥ እንደሚኖርበት በጻፉት ደብዳቤ ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡ መንግሥት ለካፒታል ፕሮጀክት አብዛኛውን ብድር የሚያገኘው ከቻይና መንግሥት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገሪቱ እየተካሄደ ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከታዋቂ ዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና እየተቸረው በመሆኑ፣ የምዕራብ የፋይናንስ ተቋማት ብድር ለማቅረብ ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡ ነገር ግን ከቻይና ሲነፃፀር፣ የምዕራብ የፋይናንስ ተቋማት የወለድ ምጣኔ ከፍተኛ ስለሆነ መንግሥት ብዙም ትኩረት እንዳላደረገ ምንጮች ይናገራሉ፡፡

Saturday, April 19, 2014

የከሸፉት የህወሓት የተስፋ ቃላት (ከለምለም ሀይሌ ኖርዌይ)

የደርግ መንግስት ከወደቀ በኋላ በእግሩ የተተካው ህወሓት ይኸው ሥልጣን ላይ ከወጣ 23 ዓመት ሊሆነው ነው። ህወሓት ወደ ሥልጣን ሲመጣ ዲሞክራሲን አሰፍናለው፣ ሰብአዊ መብት አክብሬ አስከብራለው፣ የብሔር ብሔረሰቦች መብትና እኩልነት ይከበራል፣ ልማት ይመጣል የኢትዮዽያ ሕዝብ ስደት ያበቃል፣ በቀንም ሦስት ጊዜ ይበላል የሚሉት ዋንኞቹ ነበሩ። እስኪ አንድ በአንድ እንያቸው።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/29233

Wednesday, April 2, 2014

[በአባይ ግድብ ዙሪያ የተጻፈ አጭር ሀተታ] ትንሹዋ ወያኔና ትልቁ ወያኔ አላኖሩኝም

April 2, 2014
ነፃነት ዘለቀ (አዲስ አበባ) 
ለለውጥ ያህል ከራሴ ችግር ብጀምር ምን አለበት? ግለሰብ ካልኖረ ማኅበረስብ አይኖርም፡፡ ደሞም የኔ ችግር የሁሉም ፣ የሁሉም ችግር የኔ መሆኑን የማያምን አንባቢ ቢኖር ችግር አለበት ማለት ነውና በጊዜ ራሱን ፈትሾ መድሓኒት ቢጤ ቢያፈላልግ ሳይሻለው አይቀርም፡፡TPLF is just like a Rat
ትንሹዋ ወያኔ ጠምሳኛለች፡፡ እኔን ብቻም አይደለም የጠመሰችው፡፡ ብዙዎች ኢትዮጵያውያንንም እንጂ ነው፡፡ ከወያኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ኑሯችንን እያቃወሰችው ትገኛለች – ትልቁ ወያኔ በደጅና በቤት ውስጥ እርሷ ደግሞ በቤት ውስጥ ብቻ በተናጠልና በቡድን እየተጋገዙ ወዲያ ወዲህ ውልፊት ልንል በማይቻለን ሁኔታ ወጥረውናል፡፡ ምን እንደምናደርግም ጨንቆናአለ፡፡ ይቺ የቤት ውስጥ ወያኔ ዐይጥ ናት፡፡
ዘመኑ ለይቶለት የዐይጦችና  የወያኔዎች ሆኗል ወንድሞቼና እህቶቼ ማለትም ኢትዮጵያውያን፡፡ በኔ ቤት የተረፋት ነገር የለም፤ ለወትሮው ካልሲና ጨርቃ ጨርቅ እየለቃቀመች ነበር ወደጎሬዋ እምትወስድ፡፡ ዛሬ ግን ዘመን ተቀይሮ ባዶ ሞሰብ ሣይቀር መቆርጠም፣ አልሙኒየም የምጣድ አከንባሎ መጎርደም፣ ቁም ሣጥን መቀርጠፍ ይዛለች፤ ወያኔነት ከዚህ በላይ አለ? መጽሐፎችን አንብባ ላታነብ ነገር በጥርሶቿ መከታተፍ፣ ምግቦችን ከጉሮሮዋችን እየነጠቀች ማንከት፣ በሌሊትና አንዳንዴ ደግሞ በማንአለብኝነትና ወደር በሌለው ዕብሪት በቀንም ቤትን ተቆጣጥራ ሰላምን ማወክ የዘመናችን ትንሹዋ ወያኔ ገደቡን ያለፈ የድፍረት ተግባር ሊሆን በቅቷል – ወያኔን ተማምና መሆን አለበት መቼም፡፡ ድፍረቷ እኮ ድፍረት እንዳይመስላችሁ፡፡ ኧረረረረረ…. እንዳቃጠልሽኝ የሚያቃጥል ይዘዝብሽ፡፡ ብዙ ሰዎች በርሷ እንደተቸገሩና ዘመኑ ለርሷና ለወያኔ ዓይነቶቹ ምሥጥ መሠሪዎች የሰጠ መሆኑን ይህን ችግር የማወያያቸው ሰዎች ሁሉ ይነግሩኛል፡፡
ዛሬና አሁን በኢትዮጵያ የሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 6፡30 ገደማ ሲሆን ቀን የገዛሁትን እንትን በስምንት የጦር ግምባር አጥምጄ ወደብሶት አደባባይ መውጣቴ ነው – እንዳትሰማኝና እንዳታውቅብኝ ነው የገዛሁትን ነገር በእንትን የገለጸኩላችሁ ታዲያን – እንጂ “እዚያው በላች እዚያው ቀረች” የሚል አደገኛ መርዝ መግዛቴን ለመናገር አፍሬ እንዳይመስላችሁ፡፡ ለነገሩ ወያኔና ዐይጥ ከጠላታቸው የሚከላከሉበት ብዙ ተለዋዋጭ ዘዴ ስላላቸው በበሶ ዱዔት ያዘጋጀሁትን ግብዣ እንደሚቀበሉትና እንደማይቀበሉት አላውቅም – ውጤቱን ነገ አያለሁ፤ ዲዲቲና ወባ እንኳን ተለማምደው ጓደኛሞች መሆናቸውን ቀደም ሲል ሰምተን የለም? የሆነው ሆኖ ችግሩ ቀላል እንዳይመስላችሁ፤ ከአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት የተለቀቁ ነው የሚመስሉት – እንደደፋርነታቸውና እንደሆዳምነታቸው፡፡ የሚምሩት ነገር እኮ የላቸውም፡፡ የሚሆንልኝ መስሎኝ “ዕቃ አትንኩብኝ፤ ቤቱ እንደሆነ ይበቃናል፡፡ ካለኝ አልፎ አልፎ ቀለብ እቆርጥላችኋለሁ – ከሌለኝ ግን ምን አደርጋለሁ? ብቻ አትተናኮሉኝ እንጂ እኔ መርዝ አላጠምድባችሁም፤ የዛሬን ኑሮ መቼም እናንተም ታውቁታላችሁ፡፡ ከመጠለቁ እግርን የሚፋጀው እሳተ መለኮቱ የቻይና ካልሲ እንኳን ባቅሙ ሠላሣና ዐርባ ብር በገባበት ወቅት እባካችሁን ተከባብረን እንኑር፡፡…” ብዬ ቃል ገብቼ በቤቴ ውስጥ የሚያደርሱትን ጉዳት ሰምቼ እንዳልሰማሁና ዐይቼም እንዳላየሁ ለብዙ ጊዜ ትቻቸው ነበር፡፡ እነሱ ግን የእንጀራ ሞሰብ አልጋችን ላይ አስቀምጠን ከባለቤቴ ጋር በየተራ እየጠበቅን እስክናድር ድረስ አሰቃዩን – የቤት ውስጥ ወያኔዎች! አሁን ባሰብኝና ቃሌን አፈረስኩ፡፡ እናም … የነሱስ አብነቱ ቀላል ነው፡፡ አለ እንጂ ወያኔ ለያዥ ለገራዥ ያስቸገረ! የወያኔስ ሰማያዊ መርዝ ካልተጨመረበት በምድራዊ መርዝ ብቻ አይጠራም፡፡ እናም ጎበዝ ግዴላችሁም ለላይኛውም በርትተን እንጩህ፡፡ የቃመ ብቻ ሣይሆን የጮኸም ተጠቀመ ሲባል ሰምቻለሁ፡፡
ወያኔና ዐይጥ አንድ ናቸው፡፡ ይሉኝታ አያውቁ፤ ፍቅር አያውቁ፤ ሀፍረትና ኅሊና እሚባል የላቸው፤ የተረገሙ ፀረ-ሕዝቦች፡፡
የሰሞኑ የወያኔ ኢቲቪ ወሬ የአባይ የህዳሴ ግድብ ብቻ ሆኗል፡፡ ነገሩ “አንድ ያላት እንቅልፍ የላት” ዓይነት ነው፡፡ በሌሎች ሀገራት በየአሥር ኪሎ ሜትሩ የሚገኝ ግድብ ኢትዮጵያ ውስጥ ብርቅ ሆኖ ጆሯችን እስኪደነቁርና እጅ እጅ እስኪለን ድረስ አባይን እየተጋትን ነው፡፡ ይህ ግድብ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ይልቅ ፖለቲካዊ ፋይዳው እንደሚያመዝን ቀድሞውንም የታወቀ ነው፡፡ ፈረንጆቹ አንድን ነገር “politicized” ሆኗል ሲሉ ያ እንዲያ ሆነ የሚሉት ነገር በፊት ለፊት ከቆመለትና ከሚወራለት ዓላማ ውጪ ለሌላ ጉዳይ ውሏል ማለታቸው ነው፡፡ የወያኔ የህዳሴ ግድብም ወያኔ እንደሚለው ለሀገሪቱ የሚሰጠው የተለዬ ጥቅም ኖሮ ሣይሆን ሕዝብን ለማዘናጊያነትና ሊጠቀስም ሣይጠቀስ ሊዘለልም ለሚችል የተለዬ ፖለቲካዊ ፍጆታ መሆኑን እናውቃለን፡፡ አለበለዚያ የስድስት ሺህ ሜጋ ዋት ኮረንቲ ከቁም ነገር ተጥፎ እስከዚህን ድረስ 24 ሰዓት ከበሮ የሚያስደልቅና ይቀምሰውና ይልሰው ያጣን ድሃ ሕዝብ ያለ ርህራሄ የሚያዘርፍ ሆኖ አይደለም፡፡ “አንቺ ቁም ነገርሽ የጎመን ወጥሽ” እንደምንል ወያኔም በዚህች ድልድይ ማነው ግድብ ዕንቅልፍ አጥቶ እኛንም እንደሱ አትተኙብኝ እያለን ነው፡፡
በማለፊያ ክርስቶሳዊ አባባል አንድ የአደባባይ ምሥጢር እንድናገር መልካም ፈቃዳችሁ ይሁንልኝ፤ “እውነት እውነት እላችኋለሁ” አባይ ተገድቦ ቢያልቅ በኔም ሆነ በሌሎች ወገኖቼ ሕይወት ላይ አንዳችም ቁሣዊም ሆነ መንፈሣዊ ለውጥ አያመጣም፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ፡፡ እርግጥ ነው – የተሟላ የቴክኒክ ዕውቀት ያለው የሰው ኃይል ካለና እንዳሁኑ በተጭበረበረ የግዢ ሂደት አማካይነት ፎርጅድና የአገልግሎት ዘመኑን ጨርሶ የተጣለ የማቴሪያል አቅርቦት ከተወገደ እንዲሁም የሕዝብ ብዛት በቁጥጥር ሥር ከዋለ ምናልባት ልክ እንዳሁኑ በመብራት ዕጦት ዳፍንት ውስጥ ላንገባ እንችል ይሆናል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን አሁንም ልክ እንዳሁኑ ሁሉ ለማይጠረቃው የመንግሥት ባለሥልጣናት ኪስ ማደለቢያና ለአነስተኛ የሀገር ገቢ ሲባል ቤት ያለው ሰው ሳይጠግብ ለዬጎረቤት ሀገር ኮረንቲ መቸብቸቡ ከቀጠለ የዚያኔም ቢሆን – አባይም ተገድቦ ማለት ነው – የመብራት ፈረቃው ላይቀርልን ይችላል፡፡ እናም በአባይ ግድብ ሳቢያ ከወያኔ ጋ ድብን ያለ ፍቅር የገባችሁ ወገኖች እውነቱን ከወዲሁ እንድትረዱት ላሳስብ እወዳለሁ፡፡ ወጥመድ ውስጥ ዘው ብላችሁ አትግቡ፡፡ ሀገር ካላችሁ ሁሉም አለና፡፡
ኢትዮጵያዊ መንግሥት ቢኖረን አንድ አይደለም አሥርና ከዚያም በላይ ትላልቅ ግድቦች ሊኖሩን የመቻላቸው ዕድል ሰፊ ነው፡፡ “ልማታዊ መንግሥታችን፤ ባለራዕዩና አባይን የደፈረ ጠቅላይ ሰይጣናችን ማነው ሚኒስትራችን” እያላችሁ ሟቹን ወያኔ የምታንቆለጳጵሱ ጥቅመኞች ሁሉ ዐይናችሁን ወደጭቁኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ አዙሩና እውነቱን ለመረዳት ሞክሩ፡፡ ወያኔ ከኢትዮጵያ ታሪክ አንጻር ዕድሜው የጤዛ ያህል ነው፡፡ በማታለልና በማጭበርበር 23 ዓመታትን መኖሩም የሚገርም ነው፡፡ ለዚህ ቆይታው ግን ተጠያቂው ወያኔ ብቻ ሣይሆን በተንሸዋረረ ልማት ስም አንጀታቸው ለወያኔ የሚንቦጫቦጭ አድር ባዮችና እበላ ባይ ሆዳሞች የሚያደርጉለት ሁለገብ እገዛም ጭምር ነው፡፡ የኛም አንድ አለመሆንና በሃሳብ መለያየት ለወያኔ ዕድሜ መርዘም የድርሻውን አበርክቷል፡፡ ሌላ ሌላውን ምክንያት እናንተም ታውቃላችሁ፡፡

Sunday, March 2, 2014

ጥቁር ሆኖ በኢትዮጵያውያኑ ጀግንነት የማይኮራ ባርነትን የመረጠ ብቻ ነው።

 “ … ወታደር ባለመሆኔ የጦርነቱን ውሎ ማተት አያምርብኝም፡፡ ያም ሆኖ የአድዋ ድል ዛሬ ብርቅ በሆኑብን ሁለት እሴቶች ረድኤት የተገኘ ይመስለኛል፡፡ እኒህ ሁለት እሴቶች መተባበርና መደማመጥ ናቸው፡፡ ጣልያኖቹ በጊዜው ወደ ጦርነት ሲገቡ ተስፋቸውን የጣሉት በመድፍና በጠመንጃቸው ሳይሆን ኢትዮጵያውያን ዝነኛ በነበሩበት የውስጥ መቆራቆስ ላይ ነው፡፡ የትግራይ ቅልጥም ሲመታ ሸዋ ያነክሳል ብለው አላሰቡም፡፡ በርግጥም በክፍለ ሀገሮች ውስጥ የተለያዩ ሽኩቻዎች ነበሩ፡፡ እኒህን ሽኩቻዎች አስረስቶ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ለአንድ አላማ ማሠለፍ ምኒልክነትን ይጠይቃል፡፡

“መደማመጥ ያልሁትን ላሳይ፡፡ አባ ዳኘው ከዛሬው የይስሙላ ፓርላማችን በተሻለ ሁኔታ ለልዩነቶች ቦታ የሚሰጥ ተንቀሳቃሽ ምክር ቤት በጦርነቱ ወቅት መፍጠር ችለዋል፡፡ ፀሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ በውጊያው ዋዜማ የነበረውን ሁኔታ እንዲህ ይገልፁታል

‘… አፄ ሚኒልክም በበነጋው ሰራዊቱን የቀኙን በቀኝ፣ የግራውን በግራ አሰልፈው ነጋሪትዋን እያስመቱ ወደሱ ተጓዙ፡፡ ኢጣሊያኖችም ዘበኛው ሲመጣ ባዩ ጊዜ ተመልሰው ወደ እርዳቸው ገብተው ተኙ፡፡

ከዚህ በኋላ ሰራዊቱም እንደ ኤሊ ስንመጣበት ከድንጋይ ይገባል፤ ስንመለስ ይወጣል፤ እንዲህ አርጐ ሊጫወትብን ነውን? ብሎ እጅግ አጥብቆ ተናደደ፡፡ መኳንንቶቹም ተሰብስበው ከዚህ ሰፍረን አድረን በማለዳ እዚያው ካሉበት ከርዱ ድረስ ሄደን እንዋጋለን ብለው መከሩ፡፡ ንጉሠ ነገሥቱም እሺ ብለው ድንኳኑን ለማስመጣት አዘዙ፡፡

ይህ ምክር ካለቀ በኋላ የትግሬው ገዢ ራስ መንገሻ ተሰልፎ በፈረስ ሆኖ መጣ፡፡ እሱም ይህ ምክር እንዳለቀ ባዬ ጊዜ አንድ ነገር ልናገር ይፍቀዱልኝ ብሎ ወደ ንጉሠ ነገሥቱ ቀርቦ እንዲህ አለ፡፡ እንደ ተርታ ነገር ካልሆነ ስፍራ ሄደን ልናስፈጀው ነውን? አለ፡፡ ይህ ምክር የተስማማ ምክር ሆነ፡፡ አፄ ምኒልክም ተመልሰው ከድንኳንዋ ከገቡ በኋላ እንዲህ አሉ፡፡ እንግዲህ ከሰፈሬ ወጥቶ ተኩስ አልጀመረ ባይኔ ካላየሁት ተሰልፌ አልወጣም፡፡’
 “ፀሐፌ ትእዛዝ ያቀረቡትን ዘገባ ወደ ዘመናዊ አማርኛ አሳጥሬ ሳዛውረው የሚከተለውን ይመስላል፡፡
“ርዕሰ-ብሔር ምኒልክ ሰራዊታቸውን እየመሩ ወደፊት ሲገሰግሱ የጣልያን ሰራዊት ስልታዊ ማፈግፈግ አድርጎ ወደ ምሽጉ ገባ፡፡ ምኒልክ በቀጣዩ ስትራቴጂ ላይ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ ጠሩ፡፡ በስብሰባው ላይ ወደ ጠላት ምሽግ ሄደን እንዋጋ የሚል ሐሳብ ቀርቦ ባብላጫ ድምፅ ፀደቀ፡፡ ምኒልክም በብዙሃኑ ተሰብሳቢ የቀረበውን ሐሳብ ለማስፈፀም ተዘጋጁ፡፡ ይሁን እንጂ ጄኔራል መንገሻ ዮሐንስ ዘግይቶ ስብሰባውን ከተቀላቀለ በኋላ “ምሽግ ድረስ ሄዶ መዋጋት በወገን ጦር ላይ ጉዳት ያስከትላል” ብሎ መከራከር ጀመረ፡፡ ምኒልክም “እኔ አንዴ ወስኛለሁ፤ ውሳኔዬ ካልጣመህ በሊማሊሞ በኩል ማቋረጥ ትችላለህ” ብለው ሳያሸማቅቁት ሐሳቡ እንዲጤን አደረጉለት፡፡ ሐሳቡ በድምፅ ብልጫ ፀደቀ፡፡ በድምፅ ብልጫ ያልሁት “ይህ ምክር የተስማማ ምክር ሆነ” የሚለውን የፅሐፌ ትዕዛዙን አማርኛ ተርጉሜ ነው፡፡”

Thursday, February 27, 2014

Ethiopian Airlines Co-pilot case: Interview with Attorney Shakespear Fey...

Abe Tokichaw
በአሜሪካ ሲያትል የሚገኝ እሳት የላሰ ኢትዮጰያዊ ጠበቃ አለ። ሼክስፒር ፈይሳ ይባላል። የረዳት አብራሪ
ሃይለመድን አበራ ጉዳይ ከህግ አንጻር ምን ይመስላል የሚለውን የኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክ ውየም
ከረንት አፌርስ አሁንም ውይም ኢካድኤፎች አነጋግረውት ነበር። 
ረዳት አብራሪው ጠለፋ አድርጓል ማለት አይቻልም…
ሃይለመድን ነገሩን ያደረገው ጤናው ታውኮ ከሆነ አየር መንገዱ ተጠያቂ ነው…
አበራሪው ለደህንነቴ ሰጋሁ ብሎ ያደረገውን ማድረጉ ወንጀል አይደለም፤ ሰዎች ደህንነታችውን መጠበቅ መብታቸው ብቻ ሳይሆን ህጋዊ ግዴታም አለባቸው…
ሃይለመድን ቅጣት የሚያከብድበት ሰው ላይ ጉዳት አድርሶ ቢሆን ነበር…
እና ሌሎችንም ሃሳቦችን ያነሳል። ያነጋገረው እንደልቡ ነው። በዚህ ቃል ምልልስ ጠበቃ ሼክስፒር ለአብራሪ ሃይለመድን
አበራ የህግ ድጋፍ ለመስጥት ተነሳሽነትም አሳይቷል (የሀገር ልጅ የማር እጅ ብለን እያሞካሻን!) ከኢካድ ኤፎች ዩቲብ የጠለፍናትን ቃል ምልልስ እንሆ በድረ ገጻችን፤



Tuesday, February 25, 2014

ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው


ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው (Abe Tokchaw)
በዋሽንግተን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአበራሪ ሃይለ መድን አበራ ያላቸውን ድጋፍ በሰላማዊ ሰልፈ መገልፃቸው ተሰምቷል። ሰለፈኞቹ ትላንት በስዊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ተሰለፈው፤ ሃይለመድን አበራ እንደ ወንጀለኛ እንዳይታይ የስዊዝን መንግስት ተማጽነዋል።
ሰለፈኞቹ፤ አብራሪው የዘጠና ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን  ፍትህ እጦት በአለም አደባባይ ይበልጥ ያስገነዘበ ጀግና ነው ሲሉም አሞካሽተውታል።
ባልተያያዘ ዜና
ትላንት በአዲስ አባባ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ… (በቅንፍም፤ ይህ ሚሊኒየም አዳራሽ ሲገነባ ለሚሊኒየሙ ክብረ በዓል አከባበር ለስድስት ወራት ብቻ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከማን አይቶ ቦታውን ይለቃል… ይሄው ስድስት አመቱ መጣ… ሀገሪቷን ኤክስፓየርድ ዴት የማይታወቅበት ሀገር አደረጓት እኮ…ይሄው እነ እንትና ኤክስፓየርድ ካደረጉ ስንት ጊዜያቸው ገና ከአርባ እስክ ሃምሳ አመት እንፈልጋለን ይሉናል። (በሌላ ቅንፍም ሰዉ አርባቸውን ለመብላት ቋምጧል… )) ቅንፋችንን ቀናንፈን ስንወጣ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ የሚገኘው ህብረት ባንክ አጠገብ የሚስራ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ ሶሰት ጥይቶችን ወደ ሰማይ ከተኮስ በኋላ አራተኛውን በራሱ ላይ በመተኮስ ራሱን አጥፍቷል።
ሰውየው ራሱን ከማጥፋቱ በፊት ኑሮ መረረኝ እያለ ሲጮህ እንደነበር አዲሳባ የምትገኘው ጋዜጠኛ ፂዮን ግረማ ኮረጄያለሁ።
እንግዲህ ይህንንም እብድ ነው እስኪሉን ድረስ የሃገራችን ሁኔታ የገዛ አውሮፕላን የሚያስጠልፍ የገዛ ክላሻችንን የሚያስጠጣ ሆኖ ቀጥሏል። ማለት እንችላለን።
ዜናው በዚህ አለቀ!
መከራችንም በዚሁ ባለቀ!

Henok Yeshitla Poem dedicated to Co-pilot Hailemedn Abera

Sunday, February 23, 2014

አርቲስት ራሄል ዮሃንስ ቀደም ሲል ያቀነቀነችው አንድ ዘፈን ለዘመኑ ጀግና ሃይለመድህን አበራ ከዘመናት በፊት ይህን ታሪክ አንደሚሰራ አውቃ ያቀነቀነችው እስኪመስል ድረስ፣ የግጥሙ መመሳሰል ለዚህ ጀግና ቢያንሰው እንጅ ይበዛል አያስብለም። ሊንኩን በመጫን አድምጣጩ ፍረዱ።

አርቲስት ራሄል ዮሃንስ ቀደም ሲል ያቀነቀነችው አንድ ዘፈን ለዘመኑ ጀግና ሃይለመድህን አበራ ከዘመናት በፊት ይህን ታሪክ አንደሚሰራ አውቃ ያቀነቀነችው እስኪመስል ድረስ፣ የግጥሙ መመሳሰል ለዚህ ጀግና ቢያንሰው እንጅ ይበዛል አያስብለም። ሊንኩን በመጫን አድምጣችሁ ፍረዱ።


https://www.facebook.com/photo.php?v=1425482691026703&set=vb.100006949574563&type=2&theater

Hailemariam Desalegn’s Confused Statements

February 22, 2014by Amanuel Biedemariam
On February 10, Prime Minister Hailemariam Desalegn of Ethiopia gave reporters and conducted a press conference. The statements of Hailemariam are fraught with inconsistencies and telling that there is a serious leadership vacuum and lack of direction in Ethiopia. The statements lack principle, direction and strategy. The messages are inconsistent and contradictory to previous statements.Prime Minister Hailemariam Desalegn of Ethiopia gave reporters access 

On an interview with Africa Confidential January edition, when asked what’s your Eritrea policy? PM Hailemariam Desalegn said,
“Our Eritrea policy is very clear. These two peoples are very friendly; the normalizing of relations, also with the governments, should come as soon as possible. We have accepted unconditionally the rulings [on the border] and so this has to implemented but with a discussion because the implementation process needs something on the ground since it is a colonial rather than a people’s boundary.” Emphasis added.
For a while, Ethiopians have been expressing anger and concern about the border issue between Ethiopia and Sudan claiming that the minority TPLF regime has unlawfully ceded huge chunks of Ethiopian territories to Sudan. The tenet of their argument is that the signatures of Meles Zenawi and Hailemariam Desaleng are unlawful, null and void based on Article 55(12) of Ethiopian constitution which demands accountability and ratification by parliament. On a recent article,  Ethiopia From Chopping Block”,  Dr.Alemayehu G. Mariam wrote,
“It is important to understand and underscore the fact that the “agreement” Meles and Bashir “signed”, by Meles’ own description  and admission, has nothing to do with the so-called Gwen line of 1902 (“Anglo-Ethiopian Treaty of 1902” setting the “frontier between the Sudan and Ethiopia ”). It also has nothing to do with any other agreements drafted or concluded by the imperial government prior to 1974, or the Derg regime between 1975 and 1991 for border demarcation or settlement. Meles’ “agreement”, by his own admission, deals exclusively with border matters and related issues beginning  in 1996, when presumably the occupation of Sudanese land by Ethiopians took place under Meles’ personal watch.”
Citing Wikileaks, Dr. Al Mariam writes,
“Former TPLF Central Committee member and former Defense Minister Seeye Abraha told” American embassy officials in Addis Ababa that in a move to deal with “on-going tensions between Ethiopia  and Sudan”, Meles had turned over land to the Sudan “which has cost the Amhara region a large chunk of territory” and that Meles’ regime had tried to “sweep the issue unde  the rug.”
It is unlikely that the views and efforts of the people of Ethiopia will ever see the daylight vis-à-vis the border agreements that Meles Zenawi or Hailemariam Desalegn signed or concluded since there is no question on the legitimacy of their positions by the international community. International agreements they signed will undoubtedly stand.

Saturday, February 22, 2014

Ethiopia: Abebe Gellaw Hailemedhin Abera

“በአለም ዙሪያ የሚኖር ነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወጣቱን ኢትዮጵያዊ ጀግና ሃይለመድህን አበራን በአደባባይ
መደገፍ ይገባዋል። ወያኔ በቤተሰቡ ላይ ጫና እያደርገ የሚሰራውን የከሰረ ፕሮፓጋንዳ አጥብቀን እናወግዛለን።”Abebe Gellaw

Monday, February 17, 2014

የኢትዮጵያ አውሮፕላን በገዛ ረዳቱ ጠለፋ ተደረገበት… ለምን… ?

የኢትዮጵያ አውሮፕላን በገዛ ረዳቱ ጠለፋ ተደረገበት… ለምን…  ? (ከአቤ ቶክቻው)
ዛሬ ወደ ሮም ሲበር የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን መጠለፉን ሰማን። ማነው እንዲህ የደፈረን ብለን አቶ ሬደዋንን ብንሰማቸው ጊዜ “አውሮፕላኑ ሱዳን ላይ አርፎ ነበር ምናልባት ጠላፊዎቹ ያኔ ይሆናል የገቡት” ብለው ተናገሩ።  ኋላ ላይ ሲጣራ ግን ጠላፊው የአውሮፕላን አብራሪው ረዳት  መሆኑ ተሰማ፤  ረዳቱ ጠለፋውን የፈፀመው ዋናው አብራሪ በአውሮፕላኑ መፀዳጄ ቤት ጎራ ባለበት ሰዓት ነው።
ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ…
መላ ምት አንድ፤
ዋና አውሮፕላን አብራሪው ፓይለት በሰላም እየበረረ ሳለ መንገድ ላይ የመፀዳዳት አምሮቱ መጣበት እና ረዳቱን፤ “በሰማይ የሰጠውህን በሰማይ እቀበልሃለሁ” በሚል፤ አደራ በሎት መፀዳጃ ቤት ወገቡን ሊፈትሽ ገባ። ይሄን ጊዜ ረዳቱ ሆዬ “ይሄ ሰውዬ ከመፀዳጃ ቤቱ ሲመለስ ሮም አድርሶ ከዛምም ወደ ፍትህ አልባዋ ሀገሬ ከሚመልሰኝ አሁን መሪውን እንደጨበጠኩ የራሴን እድል በራሴ ለምን አልወስንም” አለ እና … መሪውን አለቅም አለ። ሰዊስ ጄኔቭ ላይም ጥገኝነት ትሰጡኝ እንደሆን ስጡኝ ብሎ አሳረፈው።
መላ ምት ሁለት፤
ዋና አብራሪው እና ረዳቱ ቀድሞውኑ ተነጋግረው ነበረም ይሆናል። (ምንም እንኳ ይቺ ዋና አብራሪውን የምታስፎግር መላ ምት ብትሆንም ከጠረጠርን ጠረጠርን ነውና እንናገራለን)
ገና ከኢትዮጵያ ሰማይ ላይም ሳይወጡ፤ ረዳቱ እና ዋናው ኢትዮጵያ መሬት ላይ እያሉ ምሬቶቻችውን ሲያወጉ ነበር አሉ። በተለይ ረዳቱ የደረሰበትን አስተዳደራዊ በደል ሁሉ ዘረዝሮ ለዋናው አብራሪ በነገረው ጊዜ ዋና አብራሪውም በረዳቱ የደረሱ በደሎች በሙሉ በሱም እንደ ደረሱ ነግሮት ስቀሰቅ ብለው ተላቀሱ። ከዛም ረዳቱ አለው፤ “ላንተ እና ለሀገሬ እግዜር መላ እንዲያበጅላችሁ እፀልያለሁ ለእኔ ግን አንድ መላ አብጅቻለሁ” አለው። ቀጠለናም አንተ የምትተባበረኝ አንድ ነገር ብቻ ነው… ሲል ነገረው። “አንተ የሁነልህ እንጂ ችግር የለም ምን ለተባበርህ…” አለው ዋናው አብራሪ… በነገው በረራ የሆነው ቦታ ላይ መፀዳጃ ቤት ገብተህ ትንሽ ቆይታ አድርግ…! አለው አደረገም የሆነው ሁሉም ሆነ።
ከዚህ  ምን እንገነዘባለን፤
አንድ ወዳጃችን በፌስ ቡክ ገፁ “ነገ ከነገ ወዲያ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አውሮፕላን ጠለፈው ጥገኝነት ጠየቁ  የሚል ዜና መስማታችን አይቀርም” ብሎ እንደጠረጠረው በኢትዮጵያ ሰማይ ስር የደላው ማንም እንደሌለ በቅጡ  እንረዳለን። ከአውሮፕላን ረዳት እስከ ታክሲ ረዳት እና ቤተሰብ ረዳት በሙሉ በፍትህ እጦት “የተማረረበት ሁኔታ ነው ያለው”
በመጨረሻም፤
ያማንማረርባት እና የማንባረርባት ኢትዮጰያ ትመጣ ዘንድ እንፀልያለን።

Saturday, January 11, 2014

ለቴዲ አፍሮ 4.5ሚ. ብር ይከፈለዋል

በደሌ ለኮንሰርቶቹ 25 ሚ.ብር መድቦ ነበር ኮንሰርቶቹ ቢሰረዙም ውዝግቡ አልተቋጨም የቴዲ ደጋፊዎች የአፀፋ ዘመቻ ጀምረዋል
አለማቀፉ የኔዘርላንድ ኩባንያ ሄኒከን ከሚያስተዳድረው በደሌ ቢራ ጋር በመሆን በበርካታ ከተሞች ሊካሄዱ የነበሩ የቴዲ አፍሮ ኮንሰርቶች ቢሰረዙም፣ ቴዲ አፍሮ በውላቸው መሰረት 4.5 ሚ. ብር እንደሚከፈለው ምንጮች ገለፁ፡፡ እስካሁን በአገር ውስጥ ከተካሄዱ ኮንሰርቶች በላቀና ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በድሬዳዋ ተጀምሮ በርካታ ከተሞችን እንዲያዳርስ ታስቦ የተፈረመው የቴዲ አፍሮና የበደሌ ቢራ ስምምነት፤ በኢንተርኔት በተካሄደ የተቃውሞ ዘመቻ ታውኮ ነው ሳምንት ሳይሞላው የፈረሰው፡፡ ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኢንተርኔት በተሰባሰበ ድምጽ ለተካሄደው የተቃውሞ ዘመቻና ውዝግብ እንደመነሻ ሆኖ የሚጠቀሰው ዐረፍተ ነገር “የአፄ ምኒልክ ጦርነቶች ቅዱስ ናቸው” የሚል አባባል ሲሆን፤ ቴዲ አፍሮ የኔ አባባል አይደለም በማለት ማስተባበሉ ይታወሳል፡፡ በምኒልክ ጦርነት ብዙ ሰው አልቋል በሚል የገፋው ተቃውሞ፤ በደሌ ከቴዲ አፍሮ ኮንሰርት ጋር እንዳይተባበር ለሄኒከን ኩባንያ ጥያቄውን በማቅረብ እንዲሰረዝ አድርጓል፡፡
የቀድሞ የአገሪቱ ነገሥታትን በተመለከተ፣ በተለይም በአፄ ምኒልክ ዙሪያ ከየአቅጣጫው “መልካም ወይም መጥፎ ናቸው” የሚባሉ የንጉሱ ድርጊቶች እየተጠቀሱ በተደጋጋሚ የፖለቲካ ጭቅጭቆች፤ መነሳታቸው አዲስ አይደለም፤ በአንድ በኩል ምኒልክ ለአገሪቱ ነፃነት፣ አንድነትና ሥልጣኔ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል የሚሉ እንዳሉ ሁሉ፤ ስልጣናቸውን ለማስፋፋት ባካሄዱት ጦርነት ግፍ ተፈጽሟል፤ ብዙ ህዝብ አልቋል ብለው የሚያወግዙም ጥቂት አይደሉም፡፡ በመሃል ደግሞ፣ በታሪክ የተከሰቱ ነገሮችን ወደኋላ ተመልሶ መለወጥ እንደማይቻል የሚገልፁ ወገኖች፤ መጥፎ ነገሮችን እያስተካከልን መልካም ነገሮች ላይ አተኩረን እየወረስን ማሳደግ አለብን በማለት ለማስታረቅ የሚሞክሩ አሉ፡፡ ከተለያዩ አካባቢዎችና ብሔረሰቦች የፈለቁ ጀግኖች ከአፄ ምኒልክ ጋር ለአገራቸው ነፃነትና ስልጣኔ ተጣጥረዋል በማለት ከአስታራቂዎቹ ወገን የተሰለፈው ቴዲ አፍሮ፤ የምኒልክን መቶኛ ሙት ዓመት በማስመልከት ለ“እንቁ” መጽሔት በሰጠው ቃለ ምልልስ፣ ካለፈው ዘመን የሚወረሱ መልካም ታሪኮችን ጠቅሶ፣ የስህተቶችና የጥፋቶች መድሃኒት ፍቅር ነው በማለት የዘረዘራቸው ሃሳቦች ታትመው ወጥተዋል፡፡
“የአፄ ምኒልክ ጦርነቶች ቅዱስ ናቸው” የሚል ሃሳብ ግን እንዳልተናገረና በመጽሔቱ እንዳልታተመ በመጥቀስ ያስተባበለው ቴዲ አፍሮ፤ በኢንተርኔት የተሰራጨው አባባል እኔን አይወክልም ማለቱ ይታወሳል፡፡ የበደሌ ቢራ ባለቤት የሆነው የአለማችን ታዋቂ ቢራ አምራች ኩባንያ ሄኒከን፤ የበደሌ ቢራ ፋብሪካ እና የቴዲ አፍሮ ስምምነት እንዲሰረዝ የወሰነው፤ እንደብዙዎች ኩባንያዎች ሁሉ አደባባይ በወጣ ውስብስብ የፖለቲካ ውዝግብ ውስጥ መዘፈቅ ባለመፈለጉ እንደሆነ ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡ እነዚሁ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት፤ በደሌ ቢራ “የፍቅር ጉዞ” በሚል ስያሜ ከዚህ ሳምንት ጀምሮ በበርካታ ከተሞች በተከታታይ ለሚካሄዱ ኮንሰርቶች 25ሚ. ብር ገደማ መድቦ ነበር፡፡ በደሌ 4.5 ሚ. ብር ለቴዲ አፍሮ ለመክፈል ተስማምቶ ውል ሲፈራረም 1.5 ሚ ብር የመጀመሪያ ክፍያ እንደፈፀመ የገለፁት እነዚሁ ምንጮች፤ በተለያዩ ከተሞች የሚቀርቡት ኮንሰርቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ድምቀትን የተላበሱ ለማድረግ ከ20 ሚ. ብር በላይ ወጪ ለማድረግ ተዘጋጅቶ ነበር ብለዋል፡፡ በደሌ ቢራ በራሱ መሪነት በሚያዘጋጃቸው ኮንሰርቶች ላይ፣ ከትኬት ሽያጭ የሚሰበሰበውን ገቢ ለበጐ አድራጐት ድርጅቶች ለመለገስ ሃሳብ እንደነበረውም ምንጮቹ ጠቅሰዋል፡፡
በደሌ ከኮንሰርቶቹ ዝግጅት ራሱን ለማግለል ሲወስን፣ ቀደም ሲል የተፈራረመውን ውል በሚመለከት ከቴዲ አፍሮ ጋር ተደራድሮ የውል ማፍረሻ ስምምነት መፈራረሙንም ምንጮቹ ገልፀዋል፡፡ የስምምነት ማፍረሻ ስምምነቱንና የክፍያውን መጠን በተመለከተ በደሌ እና ቴዲ አፍሮ ዝርዝር መግለጫ ካለመስጠታቸውም ባሻገር፣ ከሁሉም ወገኖች መረጃ ለማግኘት የተደረጉ ሙከራዎች አልተሳኩም። በድርድር የተቋጩ ጉዳዮች ላይ ተዋዋይ ወገኖች ጉዳዩን በተናጠል በይፋ ላለመግለጽ መስማማታቸው የተለመደ እንደሆነ ምንጮቹ ጠቅሰው፤ በደሌ የመጀመሪያ ክፍያውን ጨምሮ ለቴዲ አፍሮ 4.5 ሚ. ብር የሚከፍል መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ ብለዋል፡፡ በኢንተርኔት ሲካሄድ የነበረው ዘመቻ፣ የበደሌ እና የቴዲ አፍሮ የስምምነት ውል ከፈረሰ በኋላ ቢረግብም፤ ያንን ተከትለው የመጡ ሌሎች ዘመቻዎች መፈጠራቸው አልቀረም፡፡ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት ለመቃወም የተጀመረው ዘመቻ፣ በተቃራኒ ኮንሰርቱን በመደገፍ ከተፈጠረው ሌላ ዘመቻ ጋር እንካ ሰላንቲያው ቀጥሏል፡፡ በቅርብ ጊዜ የሚካሄድ ኮንሰርት ባለመኖሩ ጭቅጭቁና ዘመቻው ምን ያህል የፌስቡክ ዕድምተኞችን ሳያሰለች ሊቀጥል እንደሚችል ገና አልታወቀም፡፡
source: Addis Admas