Tuesday, February 25, 2014

ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው


ዜና በጨዋታ፤ ከረዳት አብራሪው እስከ ዋና ጥበቃ ሰራተኛው (Abe Tokchaw)
በዋሽንግተን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአበራሪ ሃይለ መድን አበራ ያላቸውን ድጋፍ በሰላማዊ ሰልፈ መገልፃቸው ተሰምቷል። ሰለፈኞቹ ትላንት በስዊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ተሰለፈው፤ ሃይለመድን አበራ እንደ ወንጀለኛ እንዳይታይ የስዊዝን መንግስት ተማጽነዋል።
ሰለፈኞቹ፤ አብራሪው የዘጠና ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን  ፍትህ እጦት በአለም አደባባይ ይበልጥ ያስገነዘበ ጀግና ነው ሲሉም አሞካሽተውታል።
ባልተያያዘ ዜና
ትላንት በአዲስ አባባ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ… (በቅንፍም፤ ይህ ሚሊኒየም አዳራሽ ሲገነባ ለሚሊኒየሙ ክብረ በዓል አከባበር ለስድስት ወራት ብቻ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከማን አይቶ ቦታውን ይለቃል… ይሄው ስድስት አመቱ መጣ… ሀገሪቷን ኤክስፓየርድ ዴት የማይታወቅበት ሀገር አደረጓት እኮ…ይሄው እነ እንትና ኤክስፓየርድ ካደረጉ ስንት ጊዜያቸው ገና ከአርባ እስክ ሃምሳ አመት እንፈልጋለን ይሉናል። (በሌላ ቅንፍም ሰዉ አርባቸውን ለመብላት ቋምጧል… )) ቅንፋችንን ቀናንፈን ስንወጣ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ የሚገኘው ህብረት ባንክ አጠገብ የሚስራ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ ሶሰት ጥይቶችን ወደ ሰማይ ከተኮስ በኋላ አራተኛውን በራሱ ላይ በመተኮስ ራሱን አጥፍቷል።
ሰውየው ራሱን ከማጥፋቱ በፊት ኑሮ መረረኝ እያለ ሲጮህ እንደነበር አዲሳባ የምትገኘው ጋዜጠኛ ፂዮን ግረማ ኮረጄያለሁ።
እንግዲህ ይህንንም እብድ ነው እስኪሉን ድረስ የሃገራችን ሁኔታ የገዛ አውሮፕላን የሚያስጠልፍ የገዛ ክላሻችንን የሚያስጠጣ ሆኖ ቀጥሏል። ማለት እንችላለን።
ዜናው በዚህ አለቀ!
መከራችንም በዚሁ ባለቀ!

No comments:

Post a Comment