Monday, October 7, 2013

ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም

ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም

ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ አዲሱ ዬኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን ስንሰማ የስራት ለውጥ ለናፈቀን ኢትዮጵያውያን ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም የሚለውን የሃገራችን ብሂል ሳናስታውስ ኣንቀርም።



እኛን የናፈቀን መች የፕሬዝዳንት መለዋወጥ ሆነና፣ነገር ግን የኢትዮጵያን ህዝብ የራበው ሰላምና ፍት ህ የሰፈነባት ኢትዮጵያን የሚያስተዳድር አዲስ አሰራርና የስራት ለውጥ ነው እንጅ፣ ከውጭ አምባሳደሮች የሻይና ቡና አጣጭ እንዲሁም ከችግኝ ተከላ ያላለፈ ፕሬዝዳንትነት ለራሱ ካልሆነ በስተቀር ለሃገራችን ለውጥ ያመጣል ብዬ አላስብም።


ለማንኛውም ለቀድሞው ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ እንኳን ከቤተመንግስት ወደ ሌላኛው ቤተመንግስቶት አሸጋገሮት፣እንዲሁም ሌዲሱ ፕረዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ደግሞ መልካም የችግኝ ተከላ እና የ ሪባን መቁረጫ ግዜ ይሁንሎት እላለሁ።

ለምለም ከ ኖርዌይ

ታማኝ እና ቴዲ ትላንት ምሽት በስልክ አወሩ ምንጭ (ክንፉ አሰፋ)

ትላንት ምሽት። እለተ እሁድ፤ ኦክቶበር 6፣ 2013። ታማኝ በየነ እና ቴዲ አፍሮ በስልክ አወሩ። ንግግራቸው ከወትሮው የተለየ አልነበረም። እንደቀድሞው እየተቀላለዱ ይሳሳቃሉ። ታማኝ ከዴንቨር-ኮሎራዶ፣ ቴዲ ደግሞ ከሲድኒ-አውስትራሊያ በስራ ላይ ነበሩ። በዚህ የሶስትዮሽ የስልክ ጨዋታ ላይ እኔና ጴጥሮስ አሸናፊም ገብተናል።


ያን ሰሞን በኢትዮጵያ ድረ-ገጾች፣ በተለይ ደግሞ በፌስቡክ እና ሌሎች ማህበራዊ መድረኮች ላይ የውይይት ርእስ ሆኖ ሰነበተ። የታማኝ እና የቴዲ ጉዳይ። በዚህ ዙርያ የነበረው ውይይት በወዳጆቻቸው ዘንድ በጥቂቱም ቢሆን ግርታ መፍጠሩ አልቀረም። አንዳንዶች ለሁለቱም የጥበብ ሰዎች ካላቸው ፍቅርና አድናቆት ሲወያዩ ሰነበቱ። ሌሎች ደግሞ ክስተቱን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለመቀየር ሞከሩ። ጉዳዩ በእጅጉ አሳስቧቸው ለነገሩ እልባት ለመስጠት እንቅልፍ ያጡም ነበሩ። 

ሙሉውን ለማንበብ  ሊንኩን ይጫኑ