Saturday, October 5, 2013

እምቢ በል እምቢ በል ለፍቅር አንደኛ ከነኩን አርበኛ !!!!!!!!!!!!!!!!

ይህ ከሰሞኑ የወጣ ''ማነው ሚለየው ይህ ትውልድ ፍም እሳት ነው'' የተሰኘው የናትናኤል እና የጃኪየጋራ ሙዚቃ ባሳለፍነው ቅዳሜ ሴፕቴምበር 28, 2013 በኖረዎይ ኦስሎ የተደረገው የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ካየሁትና ካስተዋልኩት ነገር ጋር አንድ ሆነበኝና ዘፈኑን ደግሜ ደጋግሜ ባዳምጠውም አልወጣልሽ አለኝ።


ይኸውም በቦታው የነበርን ሰዎች እንዲሁም ዝግጅቱን በቀጥታ በ ፓልቶክ የተከታተልን ሰዎች እነደምናስታውሰው በአይነቱ ለየት ያለና እጅግ በጣም የደመቀ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እነደነበር ይታወሳል።በእለቱም ከነበሩት የክበር እንግዶች የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል ዋና አዛዥ ኮማንደር  አሰፋ ማሩ በተጨማሪ ከተለያየ የኖርዎይ ክፍለ ሃገራት የመጡ ታዳሚዎች እና ከ ኖርዎይ ውጭ ከሌሎች የ አውሮፓ አገሮች የመጡ አገር ወዳዶችም ተገኝተዋል።
ፕሮግራሙን በይበልጥ ያማረና የደመቀ ካደረጉት ነገሮች አንዱም ለክብር እንግዶቹ የተደረገላቸው በወጣት ታጋዮች ወታደራዊ አለባበስና ስርአት የቀረበው ወታደራዊ አቀባበል ሲሆን እነዲሁም በየሰዉ እጅ ሲውለበለብና ሀገራዊ ስሜትን ሲቀሰቅን የነበረው የ ኢትዮጵያ ባንዲራ ነው።


በዚህም ቀን በተደረጉት የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች 48,633 የኖርዌጅያን ክሮነር የተገኘ ሲሆን ። ይህ ገቢ ከምግብ ሺያጭ ፣ ከመግቢያ ትኬት፣ ከቲሸርት ሺያጭ እንዲሁም ከተለያዩ ባህላዊ ቁሳቁሶች ሺያጭ ሳይጭምር መሆኑ ይታወቃል። ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ ሀገራዊና ፖለቲካዊ ውይይቶች ተደርገዋል።
 በዝያም ቀን በሰው ሁሉ ፊት ላይ ያነበብኩት ነገር ቢኖር ከፍተኛ የሆነ ይሀገር ፍቅር ስሜት እንዲሁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለማምጣት የሚሻ ልብ በነዚያ በፍም እሳትና በማይደፈሩ ትውልዶች አይን ላይ ሳይ የተሰማኝ ስሜት የዚህ ትውልድ አንዱ ኣካል በመሆኔ ከፍተኛ ኩራት ነው። እውነትም ፍም እሳት ለወያኔ የእግር እሳት።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !
ለምለም ሀይሌ ከኖርዌይ 

MUST WATCH!!!ኣሰቃቂ ሞት በሊብያ ሳህራ by ዲጄ ቶም

https://www.facebook.com/photo.php?v=149761338471526

በመጀመርያ ለዚች ቀን ላበቃኝ እግዚኣብሔር ይመስገን በእርግጥ ያለፈውን ስቃይ ሳስበው ለዚች ቀን እደርሳለው የሚል ተስፋ ኣልነበረኝም በቦታው ሆነህ ስታየው በታም ከባድ ነው በዚ ሰኣት ህሊናዬ ላይ ድቅን የሚልብኝ ኣንድ በጣም የምወደው ጓደኛዬ ነው ሁለታችንም ኣንድ ኣይነት ፍልስፍና ነበረን እሱም [ጉዞዬ ረዥም ፣ ተስፋዬ ሩቅ ፣ችግሬ ብዙ ነው ] የሚል ሁለታችንም በጣም ከምንወደው መጽሃፍ ከ ዣንቫልዣ (ምንዱባን) የወሰድነው ኣባባል ነበር። አሱ ወደ ሩቅ ተጉዞዋል እኔ ግን ኣለሁ።

Click the above facebook link to watch the video.

DJ TOM

Wednesday, October 2, 2013

ግንቦት7 በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ መስመሩን እየዘረጋ መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ

 ግንቦት7 በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ መስመሩን እየዘረጋ መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ
መስከረም ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸው ይህንን የተናገሩት በኖርዌይ ከተካሄደው ደማቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሁዋላ ነው።
የግንቦት7 ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቱ በአንድ በኩል በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል አባላት ላይ ከፍተኛ መነቃቃት የሚፈጥር በሌላ በኩል ደግሞ የተጣለብን ህዝባዊ አደራ ከፍተኛ መሆኑን የሚያስታውሰን ነው ብለዋል።
በቅርቡ ከኢትዮጵያ አየር ሀይል ከድተው የሄዱት ሰዎች በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኙ የገለጹት አቶ አንዳርጋቸው ፣ በመከላከያ ሰራዊት በእግረና፣ በአየር ሃይልና በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ሊደርሱበት በማይችሉበት መንገድ መስመር እየዘረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በውጭ አገራት ተመሳሳይ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ለማድረግ እቅድ አላችሁ ወይ ተብለው የተጠየቁት አቶ አንዳርጋቸው፣ ህዝባዊ ሀይሉ ከተግባር ጋር በተዛመደ መልኩ የገቢ መሰባሰብ ዝግጅት መርሀ ግብሩን ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በህዝባዊ ሀይሉ ወይም በግለሰቦች ስም ምንም አይነት የገቢ መሰባሰቢያ ዝግጅት መደረግ እንደሌለበት ገልጸዋል
በሌላ ዜና ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላቸው በስቶክሆልም እና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር ውይይት አድርገዋል። አቶ አንዳርጋቸው የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይልን ዓላማዎች፡ተልዕኮዎች እና ራዕይ በማስተዋወቅ ህዝባዊ ሃይሉ ከምስረታ ጀምሮ አሁን ያለበትን ደረጃ በምስልና በጽሁፍ የተደገፈ ገለጻ ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።
እሳቸው እና ሌሎች የአመራር አካላት እንዲሁም አባላት የተገኙበት የውትድርና ስልጠና አንዱ የበታች አንዱ የበላይ እንዳልሆነ በማስገንዘብ ይህ ህዝባዊ ሃይል ቤተሰባቸውን፡ስራቸውን፡ ገንዘባቸውን፡ እና የተደላደለ ኑሯቸውን በመተው ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን የተዋቀረ እንደሆነ ገልጸዋል።
የግንቦት ሰባት ዓላማ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ማስፈን ብቻ ሳይሆን ባለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያውያን የተገፈፉትን ክብራቸውን ማስመለስ ጭምር መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው አስምረውበታል ሲል ቴዎድሮስ አረጋ ከስዊድን ዘግቧል።
ESAT